ቡራኬ ክፍል ፬
ለሕዝቦች ሁሉ::
(ብላቴናው ዘመድዎ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ቁጥር 5 መሠረት ከዚህ በታች እርስዎ የሚቀበሉትን በጎ የበረከት ቃላት በክርስቶስ ኢየሱስ ስም ተናገርኩ - “...ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና ...” የሚለውን የጌታን ቃል ዘመድዎ ስረዳው : - በ-እኔ ከሆናችሁ ግን ፣የ-እኔ ከሆናችሁ ግን ፣
ለ-እኔ ከሆናችሁ ግን ፣ከ-እኔ ከሆናችሁ ግን ሁሉንም ነገር ማድረግ ትችላላችሁ:: ክብር ለስሙ ይሁን :: ጸሐፊው እጅጉን አሜን ይላል ::
ቡራኬ ››
›› ለእግዚአብሔር አምላክ ለልጁም ለኢየሱስ ክርስቶስ አጋዣችንና ወደ እውነት ሁሉ መሪያችን ለሆነው ለጌታ መንፈስ ቅዱስም ክብር ይሁን::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ::
›› የተጣመመች ነፍስ ያለችን እኛ ሁላችን ነፍሳችን በጌታ በኢየሱስ ስም ትቃናልን::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ::
›› አንድ እግራችን ቤተክርስቶስ ውስጥ አንድ እግራችን በድቅዱ ጨለማ(በዓለም ውስጥ) የተንሸራተተብን ሁላችን በጌታ ስም እግራችን ወደ ሰላም ሕይወት ጤና ቤት ይመለስልን::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ::
›› እናንት በዓለም ላይ በመዝናናት ላይ ያላችሁ እየመሰላችሁ በመባለግ ብክነት ጉዳት ላይ ያላችሁ በሙሉ ባላችሁበት እንድትቆሙ እናዛለን::ከድቅድቁ ጨለማ ኑሯችሁ - ቅሌን ጨርቄን(ገንዘቤን ንብረቴን...አክስቴን አጎቴን ...) ሳትሉ ወደ ሚደነቀው ብርሃናችሁ ወደ ክርስቶስ ኢየሱሳችሁ ዛሬ በመዳን ቀን ዘወር እንድትሉ እንመክራለን::
[ሰዎች ሁሉ ወደ ክርስቶስ ዘወር ይላሉ::
(የቤት ልጆችም ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ (ወንጌል ይሰብካሉ ፣ይመሰክራሉ፣ወንጌል ሰባኪዎችንም
በጸሎታቻው ያግዛሉ ፣ ይደግፋሉ
ሠራተኞችም ደግሞ የቅሌስ የጨርቄስ ጉዳይ
ለእኔስ የእኔስ እያሉ እንዳይተክዙ
ከቅላቸው እና ከጨርቃቸው ያካፍላሉ ::]
›› ሥራ አጥተን የምንንከራተት እኛ ሁላችን ሥራ እናገኝ ዘንድ በጌታ ስም ይሁን::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን›› ይላሉ::
[ይህ ቡራኬ ስራ እናገኝ ዘንድ
(በእናት አገር ቢሆን በዳያስፖራ ብንኖር)
ፍላጎተኞች እንድንሆን ያዛል::
ወይ ወደ ስራ ፍለጋ ወይ ወደ ስራ ፈጠራ
እንድንሰማራ አክሎ ያስረግጣል::]
›› የጌታ እግዚአብሔርንም ስራ አብዝተን በመስራት ላይ ያለን እኛ ሁላችን አጥርተን ደግሞ እንድንሰራ የሚደነቀው ብርሃን
በአገልግሎታችን በሕይወታችን እጅጉን ይብራልን::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ::
›› ቀን በሀሳብ ትካዜ፣ምሽት በፍራት ድንጋጤ፣በመንፈቀ ሌሊትም በቅዠት ኩነኔ የምንረበሽ ሁላችን የክርስቶስ ኢየሱስ ዘላለማዊ ሠላም እንደወንዝ በልባችን ይፍሰስ ፤ ምንጩንም እልባችን ያድርግ::
ሕዝቦች ሁሉ ‹‹አሜን››ይላሉ::
(እባክዎ “ሠላምህ እንደወንዝ በልባችን
ፈሰሰ ምንጩን እልባችን አደረገ...”
የሚለውን መዝሙር ይጋበዙ::)
›› ሕዝቦች ሁሉ ክብር ለስሙ ለጸሐዩ ንጉስ ለክርስቶስ ኢየሱስ የአምላክ ልጅ ይሁን ይላሉ::
ሕዝቦች ሁሉ አሜን ይላሉ::