»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Monday, 24 June 2013

የሠላሙ አምላክ ከእኔ ጋር ነው

ማይ ላይፍ ኢዝ ኢን ኤ ሜስ
አይ ዶንት ኢቭን ኖው 
ሀው አይ ዊል ጌት አውት ኦፍ ዚስ
ብሎ እያለ ጥቂት ሲቀረው በአያሌው ሊተክዝ

"የሠላሙ አምላክ ከእኔ ጋር ነው 
የሠላሙ ንጉስ ከእኔ ጋር ነው 
አልታወክም በሚሆነው 
አልታወክም ሊሆን ባለው"

የሚል የጥንት ዘመን መዝሙር 
ወደ ልቡ ትዝታ ተሰጠው::

***
ሆኖም ቢሆን ግን ለወንድሞች ተግሳጽ ይሆን ዘንድ ብሎ በበጎ ልቡና  ከወንድሞችም ፍቅር  የተነሳ "...ለዚህ ሁሉ የተዳረኩት..." ሲል ለንስሃ በሚያበቃ የዝታ ፀፀት መገረፉን ለጉባኤው መደበቅ አልፈለገም:: "...ኣዎና በጸሎት አልተጋሁም ነበርና፣ቃለ እግዚአብሔርን ማንበብ እጅጉን ቸል ብዬ ነበርና፤መጾምን በሰበብ አስባብ፣ በስጋ ድካም ፣በሆዳምነት ...ወዘተ መጾምን አልጾምኩም ነበርና ፤አብዝቶ አገልጋይ ፣ሯጭ ፣ተሯሯጭ ፣ሰባኪ ፣ተናጋሪ ፣ጸሐፊ ፣አንባቢ ሆኜ መታዘዝ ከመስዋዕት ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ እንደሚበልጥ መገንዘብ ብቻ ተስኖኝ ነበር እንጂ..."ሲል ለጉባኤው አስረዳ::በጉባኤው መረብ ብዙ ሺህ ሕዝብ ነበር::

ሂዝ ሜርሲ ኢንዱረስ ፎር ኤቨር::

ክብር ለስሙ ይሁን::

No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።