»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Monday, 29 July 2013

እግዚአብሔር ሆይ እንዴት ድንቅ ነህ

እግዚአብሔር ሆይ እንዴት ድንቅ ነህ
ነፍሳችን ረካች በጉብኝትህ
ጥያቄያችንም ተመለሰልን
ስምህ ይባረክ ከፍ ይበልልን

ጠላት ጠፍሮ ፍጹም ተብትቦ
እንዳናመልክህ ዙሪያው ተከቦ
መሰንቆአችንን ከሰቀልንበት
ዛሬ አውርደን ንገስ አልንበት
አዝ….

እኛስ ቆዝመን አዝነን ነበር
ማየት ተስኖን ከሞት ባሻገር
በትንሣኤው ኃይል ደስታን ሞልተኸን
በባዕድ ምድር እንዘምራለን
አዝ….

ከአቻምና አምና ከአምናም ዘንድሮ
ያንተ ቸርነት ስንቱ ተቆጥሮ
ስንቱን ጨለማ አሸጋገርከን
ከምንገምተው በላይ ሆንክልን
አዝ…
...የሚል የጥንት ዘመን መዝሙር ትዝ አለኝ። እባክዎ ይበሉ ይቀጥሉ እርስዎ ይዘምሩ እንጂ።
***
http://www.zimmare.com/song.php?s=s&i=2052a07c

No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።