»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Sunday, 15 September 2013

ቤቴስ ምንድነው ከጣሪያዬ በታች ኢየሱስ የገባው

Hewane Luv & Life Gardens » Song of the Week » ምህረት የበዛለት በዳግማዊ ጥላሁን::
ኧረ እኔ ማነኝ ቤቴስ ምንድነው 
ከጣሪያዬ በታች ኢየሱስ የገባው (2) 
ምህረት የበዛለት ፍቅር ይቅር ያለው 
ደሞ ያየ ቸርነቱን እንደኔ ያለ ማነው (2) ...

 (እኔማ) ሞተ ስባል ያለሁ 
(እኔማ) ጠፋ ስባል የቆምኩ
 (እኔማ) ምንም እንዳላየ
 (እኔማ) እንዴት ዝም እላለሁ
 (እኔማ) እኔማ ስላንተ
 (እኔማ) ለሀገር ለምድሩ
 (እኔማ) አልጠግብ አውርቼ 
(እኔማ) ምህረት አግኝቼ 

ምህረት የበዛለት... 

በምህረትህ ብዛት ቤትህ እገባለሁ 
አንተ ራርተህልኝ እኔም ሰው ሆኛለሁ (2)
 አቤቱ የወደቀውን እንዴት አየኸው
 አቤቱ የተረሳውን እንዴት አሰብከው 
ምህረትህ ምህረትህ እጅግ ብዙ ነው
 ፍቅርህ ፍቅርህ እጅግ ብዙ ነው (2) 

አቤቱ ታናሹን ሰው እንዴት አየኸው
 አቤቱ የተጠላውን እንዴት ወደድከው
 ምህረትህ ምህረትህ እጅግ ብዙ
 ነው ፍቅርህ ፍቅርህ እጅግ ብዙ ነው (2)

 (እኔማ) ያንን ዘመን ሳስብ 
(እኔማ) እንባ ይቀድመኛል
 (እኔማ) ሞት ሽረት ሆኖብኝ
 (እኔማ) ማን አለሁ ብሎኛል 
(እኔማ) ከበለሱም በታች
 (እኔማ) ድምፅህን መስማቴ 
(እኔማ) ያ ነው ሰው ያረገኝ
 (እኔማ) የመኖር ምክንያቴ

 ምህረት የበዛለት...
***

No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።