»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Thursday 9 July 2015

እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ የዘላለም : ባለውለታዬ


 አንዳንዴ : ሳስታውስ : የአለምን : ኑሮዬን
እንደተሰቃየሁ : ሳላገኝ : ጌታዬን
ሰላም : ስሻ : ስከንፍ : ስቀር : በየቦታው
ፈልጎ : አዳነኝ : የሰላሜ : ጌታ

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

የጭንቀት : ገደሌን : ልወጣ : ስቧትት
ወጥቼ : ወርጄ : ተመልሼ : ስወድቅ
ልጁን : ላከ : ለኔ : መጠለያ : ሆነን
ከረግረጉ : ኃጢያት : ባህር : ወስጥ : አወጣን

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

ስሙን : ኢየሱስ : አሉት : አዳኝ : ስለሆነ
ከኃጢያት : ልድኑበት : እርሱ : መረመረ
እኔን : አሰቃዩን : እነርሱን : ተዉአቸው
ብሎ : እነ : ጴጥሮስን : ከጉድ : አወጣቸው

አዝ:- እጄን : ይዞ : መራኝ : ጌታዬ
የዘላለም : ባለውለታዬ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ (፪x)
ሃ-ሌ-ሉ-ያ : ሃ-ሌ-ሉ-ያ

ሃሌሉያ : ሃሌሉያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ
አውጥቶኛል : ከዓለም : ገበያ
በተራዬ : ልበል : ሃሌሉያ


No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።