ሰዎች ሁሉ በመልከ እንጀራ
የሚራቡህ ረሀብ
በአምሳለ ውሃ የሚጠሙህ ጥማት
ተረዳን ዛሬ አንተ እንደሆንክ
ሰዎች ሁሉ የሚራቡት ፍቅር
አንተ ነህ
ሰዎች ሁሉ የሚረኩት ፍቅር አንተ ነህ
ሰዎች ሁሉ የሚዋቡት ውበት
የሚጠሙት ጥማት አንተ ነህ
ሰዎች ሁሉ የሚናፍቁት ሰላም
እረፍትና ምህረት
አንተ ነህ።
እልፍ ቢሉ ይህን ሁሉ እንደሆነው
ሆኖ ያገኙታል
ከዚያም ቀን ጀምሮ መኖርን ይጠሉታል።
እስከዚያው ግን የራሳቸውን መኖር ይኖሩታል።
የመለኮት ምርጫ ዕድል ጉዳይ እንደሆን
ጥርጥር የለውም አሁን በዚህ ሰፈር
ኋላ ላይ ግን ለሁሉም ነው
በሚመጣው ሰፈር።
የእግዚአብሔር ልጅ።
No comments :
Post a Comment
Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።