»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Sunday, 16 March 2014

Song of Months : ልቤን ፡ በፍቅርህ ፡ ያበስከው

1.
ሳይሳሱ ፡ ፍቅሩን ፡ ወግተው ፡ ውርደት ፡ አለበሱት
ስለፈወሰ ፡ አቁስለው ፡ ባፈቀረ ፡ ጠሉት
የደሃ ፡ አዛኝ ፡ የሆንከው ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
ይገባ ፡ ነበረ ፡ ወይ ፡ ለእኔ ፡ አፈር ልትለብስ


የእግዚአብሔር ፡ በግ ፡ የሆንከው
ልቤን ፡ በፍቅርህ ፡ ያበስከው
ጓዴ ፡ ኢየሱስ ፡ እስቲ ፡ ና
የማዋይህ ፡ አለኝና (፪x)

 2.
አንተ ፡ ፍቅር ፡ ነህና ፡ ልትጠላኝ ፡ አቃተህ
ነፍሴን ፡ ከእሳት ፡ አወጣህ ፡ እራስህን ፡ ጐድተህ
የእኔ ፡ የሆነ ፡ ምን ፡ አለኝ ፡ እራሴም ፡ የአንተው ፡ ነኝ
ስለዚህ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ደጋግመህ ፡ ለውጠኝ


3.
ኑሮዬና ፡ ተግባሬ ፡ ለእኔ ፡ ባይጥመኝም
ጠላቴ ፡ እየወጋኝ ፡ ቢያደናቅፈኝም
አንድ ፡ ጊዜ ፡ ቆርጬ ፡ ተከትዬሃለሁ
ድካም ፡ እንኳን ፡ ቢያጠቃኝ ፡ እከተልሃለሁ

4.
 ያ ፡ የምድር ፡ ጨለማ ፡ አይሎ ፡ እንዳይውጠኝ
 መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ጌታዬ ፡ ሳጠፋ ፡ ገስጸኝ
 መንበርከክን ፡ ይወዳል ፡ ሥጋ ፡ ለዓለም ፡ ነገር
 ጽናትህን ፡ እሻለሁ ፡ ከቶ ፡ እንዳልቀየር


 የእግዚአብሔር ፡ በግ ፡ የሆንከው
ልቤን ፡ በፍቅርህ ፡ ያበስከው
ጓዴ ፡ ኢየሱስ ፡ እስቲ ፡ ና
የማዋይህ ፡ አለኝና (፪x)
______
Listen to the music here:
Source: 1:
http://wikimezmur.org/am/Addisu_Worku/Kebur_Kebur/Esti_Na#.UwomhFRFDEY
Source 2:
http://www.wongelnet.com/lyrics/frame.php?albumId=31

No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።