»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

Saturday, 22 March 2014

Song of Months 2: ይልቅ ብዙ አድክሜሃለሁ የትም እየቀረሁኝ

ለምን ወደድከኝ አልልህም በእርግጥ ወደሀኛል
የፍቅርህ መግለጫ ይሄ ነው ለኔ ተወግተሃል
አንተ ለኔ የሆንከውን ያህል እኔ ላንተ አልሆንኩም
ምን ያህል እንደሆን አላውቅም ለክቼ አላየሁም

ግን አንድ ነገር አውቃለሁ
ስለወደድከኝ ወድሃለሁ
ከእርግማን ስለዋጀኸኝ  ሞተህ ሸክሜን ስለወሰድክ
በመንፈስ ቅዱስ ስለሞላኸኝ ነፍሴን ስለባረክ
ጸጋህን አብዝተህ ስለሰጠኸኝ ከቶም ስላልተውከኝ
ምን ያህል እንደሆን አላውቅም ለክቼ አላየሁም

ግን አንድ ነገር አውቃለሁ
ስለወደድከኝ ወድሃለሁ

ደስ ላሰኝህ እቀናለሁ በህይወቴ ላከብርህ
ሆኖም ከቶ አልጠቀምኩህም ሁሌ ሳሳዝንህ
ይልቅ ብዙ አድክሜሃለሁ የትም እየቀረሁ
ዙ ላላፈራሁ ኢየሱስ ከፍቶኝ አልቅሳለሁኝ
***
ክብር ለዘለዓለም ክብር ለስሙ።

No comments :

Post a Comment

Comment.Share.ይሳተፉ እንጂ።